ጉዞ ጉራጌ ፌስቲቫል እና ቫኬሽን ፕሮግራም

ጉራጌን በ ኢንቨስትመንት የማነቃቃት አላማ ያለው

የጉራጌን ቱሪዝም የማነቃቃት አላማ ያለው "ጉዞ ጉራጌ 3 " በደማቅ ሁኔታ ሊካሄድ አስራ አምስት ቀናት ቀርተውታል። ይህ ጉዞ ከእስከአሁኑ በተለየ መልኩ ሙሉ ለሙሉ የክብር እንግዶችን ብቻ በመያዝ ወደ ጊቤ ፓርክና አካባቢው የሚደረግ ጉብኝት ና ካምፒንግ ነው።

አዳዲስ ነገሮች እንሞክራለን ካምፒንግ አርጎ በደን መሀል ክትፎ እንበላለን። ክትፎ ጫካ ልትገባ ነው😂 ከተፈጥሮ ሀብት አልፈንም የጉራጌ ህፃናት እየተማሩባቸው ያሉ ትምህርት ቤቶችን ና እናቶች ቀድተው የሚጠጧቸውን ወንዞች እናያለን። የጉራጌ ሁለት መልኮች 🤔

  1. የጉዞ ጉራጌ ተጨማሪ ስራዎች

    የጉዞ ጉራጌ ተጨማሪ ስራዎች

    ቱባ ባህል ወዳለበት ጉራጌ ለመሄድ እየፈለጉ የሚወስደኝ ሰው አጣሁ ብሎ መማረር ቀረ።

    ከወር በፊት የማይረሳ ጉዞ ወደ ጉራጌ ያደረገው ጉዞ ጉራጌ አሁንም በመስቀል ወደ ጉንችሬ ያመራል። ከመስከረም 15 እስከ መስከረም 17 ከጎመን ክትፎ ጀምረን እስከ ሻኛ ድረስ ሁሉንም ባህል አብረን እንታደማለን።

    ክትፎ ለመጠጣት ዝግጁ ናችሁ ?

    ጥሬ ስጋ ፣ ክትፎ ፣ ጎመን ክትፎ ፣ ዝማሞጃት ...አንድም የሚቀር የለም።

    ባህላዊ ደመራን በጀፎረ መንፈሳዊውን ደመራ በቅዱስ ዮሀንስ ቤተክርስትያን ታድመን። በአዛውንቶች ስኬት በስኬት የሚያደርግ ምርቃት ተመርቀን አመቱን በደስታ እንጀምረዋለን።

  2. ለሚስኪኖች መድረስ ከሚስኪኖች ማዕድ መጋራት

    ለሚስኪኖች መድረስ ከሚስኪኖች ማዕድ መጋራት

    በ "ጉዞ ጉራጌ" የተለያዩ እንግዶች ጋዜጠኞችንና የቱሪዝም ባለሙያዎችን በግብዣ ...10 ተጓዦችን ደግሞ በክፍያ ወደ ጉንችሬ ወስደን በዓሉን ደስ በሚል ሁኔታ አሳልፈናል። ሁሌም ጉዞዎች ሲዘጋጁ በነዋሪው ህዝብ ላይ ድሎትንና መዝናናትን ከማሣየት ባሻገር ነዋሪውንም ማገዝና ማሣተፍ ግድ ነው ብለን ስለምናምን የጉዞው ማጠናቀቂያ አቅም ለሌላቸው ሀያ ቤተሰቦች በሬ ለብቻቸው ገዝተን በክብር ማቀራጨት ነው።

    ለዚህም እስከ አሁን ድረስ ከእኛም ከእናንተም 40 ሺ 300 ብር ማሠባሠብ ችለናል። የነገ አላማችን እንዲሳካ ዛሬ ባየነው ገበያ 55 ሺ ብር ገደማ ያስፈልገናልና የቀረንን 15 ሺ ብር ለመሸፈን 150 ሰዎች መቶ መቶ ብር እንድታግዙን እንጠይቃለን።

    ዘንድሮ በሚዲያ የጀመርነው ስራ ቀጣይ አመት ተስፋፍቶ ወደ ጉራጌ ሀገር የመስቀል የቱሪዝም ጉዞዎች በየሰፈሩ አንዳንድ ወይፈን ለተቸገሩ ሰዎች የሚገዛበት ሁኔታ እንደሚፈጠር ተስፋ እናደርጋለን። በተለይም ዘንድሮ ለአረፋ ባዘጋጀነው የአረጋውያን እገዛ ቻሌንጅ በብዛት የተሣተፉት ክርስትያኖች አሁን ለመስቀል እያዘጋጀን ባለነው ቻሌንጅ ደግሞ አብዛኛው ተሣታፊዎች ሙስሊም ቤተሰቦቻችን መሆናቸው አስደስቶናል። ተጠናክሮ እንዲቀጥል የምንፈልገውም ይሄን ህብረትና አንድነት ነው።

    በቀሩት ሰአታት 150 ሰዎች ፈልገናል አለሁ በሉን 🙏

የት መሄድ ይፈልጋሉ?

የአረቅጥ ሀይቅ በጉራጌ ዞን በአረቅጥ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ይገኛል፡፡

ሀይቁ ከአረቅጥ ከተማ በስተ ሰሜን ምስራቅ በ1 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
በተንጣለለ መሬት ላይ የሚገኘው የአረቅጥ ሀይቅ ከወልቂጤ ከተማ በ68 ኪሎ ሜትር ከአዲስ አበባ 219 ኪሎ ሜትር ርቀት ይገኛል፡፡
ሀይቁ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ለአሳ ምርት፣ለመዝናኛም ያገለግላል።134.5 ሄ/ር ላይ ተንጣሎ ሚገኘው ሀይቁ አማካኝ ጥልቀቱም 2-5 ሜትር እንደሚደርስ ይገመታል።
ይህ ሀይቅ ከወልቂጤ ወደ ሆሳዕና በሚወስደው የአስፋልት መንገድ በቅርብ ርቀት ከመገኘቱም በላይ በክረምት ውሃው ሙልት ብሎ በዙሪያው ለአይን ማራኪ በሆኑ የጉራጌ ባህላዊ ቤቶች እና የአረንጓዴ ልማት ታጅቦና በተለያዩ የአእዋፋት ዝማሬዎች ታክሎበት ለቱሪስት ምቹና አስተማማኝ ስፍራም ያደርገዋል፡፡ በተጨማሪነትም ሀይቁ ዳር ላይ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ሙሉወርቅ ሎጅ ለቦታው ልዩ ውበትን አላብሶታል።
በበጋ ወራትም የሀይቁ መጠን የመቀነስ ሁኔታ አይታይበትም በዚህ ሀይቅ ቁጥራቸው በርከት ያሉ ዳክዎችና የተለያዩ የአእዋፋት ዝርያዎች በውሃው ተንሳፈው ሲታዩ ልዩ ውበቶች ናቸዉ ፡፡

ጉዞ ጉራጌ 3 ተጀምሯል

የጉራጌ ቀዬ አመቱን ሙሉ ደምቆ ... ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ተስፋፍቶ ለማየት

... ጉራጌው ብቻ ሳይሆን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን ምኞታችን ነው።

ድህነትና የልማት እጦት በማዘን ና በቁጭት ብቻ እንደማይፈታ እነሠምናለንና ለመፍትሄው እየተጋን ነው። የቱሪዝም መስህቦችን መፈለግ ፈልጎም ማስተዋወቅ ቱሪስቶችን መጥራት ለብዙዎች የስራ እድል መፍጠር ላይ ወጥረን እየሠራን ነው። ገና ከጅምሩ ውጤታችን ፍሬ አፍርቶ ቪድዮዎቻችን በመቶ ሺዎች እየታዩ ነው። ገና ሚሊየኖችን እንደርሳለን።

ነገና ከነገ ወዲያ በጊቤ ፓርክ የቱሪዝም ፌስቲቫል እናካሂዳለን። የሚዲያ ና የቱሪዝም ባለሙያዎች በእንግድነት ይገኛሉ። የዚህን ፕሮግራም ውጤትም ከነገ ጀምሮ በጋራ እናየዋለን።

ለዚህ ፕሮግራም እገዛ ስንጠይቅ ከሜየት አልፈው ለተግባር የፈጠኑት ጥቂቶች ቢሆን የጥቂቶች ወኔ እኛን አበርትቶናል። ከሚጠበቅብን ወጪ ገና የሠበሠብነው ግማሹን ነው ። ከዛም ውስጥ ግማሹን የሸፈኑልን ሶስት ሰዎች ጉራጌ ያልሆኑ ግን የጉራጌ ልማት ውጤቱ ለሀገር ነው ብለው የሚያምኑ ናቸው። ደስ አይልም🤔❤️

የጉራጌ ዞን አስተዳደር ፣ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፣ ወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፣ የጊቤ ፓርክ አስተዳደር ና የእኖር ወረዳ አስተዳደር የቻሉትን እየደገፉን ነው። የሁሉንም ድጋፍ ጠቅሰን እውቅና እንሰጣለን🙏

ለመልካም ብለን በተነሳንበት ጉዞ በእዳ እንዳንወድቅ ከመቶ ብር ጀምሮ በማዋጣት አለንላችሁ በሉን። መልካም መንገድም ተመኙልን🙏❤️

ንግድ ባንክ - 1000654868097

አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

TEAM GUZO GURAGE

contact us
OH HEY, FOR BEST VIEWING, YOU'LL NEED TO TURN YOUR PHONE